(ጌታቸው አሰፋ፤ ኅዳር 15 ቀን 2004 ዓ.ም.)ስለ ‘ያ ትውልድ’ና ‘ይሄ ትውልድ’ ከመጻፍ አስቀድሞ
‘ያ ትውልድ እና ይሄ ትውልድ ስንል ምን ማለታችን ነው?’ የሚለውን ጥያቄ መመለስ ተገቢ ነው። በተለመደው አባባል በ1960ቹ መጀመሪያ
አጋማሽ ውስጥ ይካሄዱ በነበሩት የተማሪዎች እንቅስቃሴዎች ወቅት እድሜያቸው ቢያንስ ለአቅመ-መሳተፍ የደረሱ ሰዎች ስብስብን ነው
‘ያ ትውልድ’ የምንለው።
ላላ ስናደርገው ….የእድሜ መስፈርቱ እንዳለ ሆኖ
ቀጥሎ ያለውን አይነት ግጥም የሚገጥም ሰው ወይም እንዲህ ተብሎ የተጻፈ ግጥምን ማንበብ አሁን ድረስ የሚመስጠው ሰው አባል የሆነበት
ትውልድ ማለት ነው ልንልም እንችላለን።