Tuesday, May 15, 2012

ኢል-ቆሻሻ

(ጌታቸው አሰፋ፤ ሚያዝያ 27 ቀን  2004 ዓ.ም.) እጅ ስልክ፤ ቴሌቪዥን፤ የጠረጴዛ ኮምፒዩተር፤ የጭን ኮምፒዩተር፤ የስሌት ማሽን፤ አታሚ ማሽን ወዘተና ሌሎች በኤሌክትሮኒክ የሚሰሩ የቢሮና የቤት እቃዎች ሲያረጁ ወይም ከጥቅም ውጪ ሆነው ሲወገዱ ስለሚፈጥሩት ቆሻሻ ነው ዛሬ የምናነሳው። ኢል-ቆሻሻ እንበለው - የእንግሊዝኛውን በቀጥታ ወስደን ‘ኢቆሻሻ’ (ቆሻሻ ያልሆነ) ብለን ጥሩ ስም ከምንሰጠው።
የኤሌክትሮኒክ እቃዎች በዘመናችን በሰው ሕይወት የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ያላቸው ሚና ከፍተኛ ከመሆኑ የተነሳ በእነሱ መጠቀም የጀመረ ሰው ከእነሱ ውጪ ሕይወት የሌለ እስኪመስለው ድረስ ጠባቃ ኑሮ እንደሚኖር ይታወቃል። አገራችን የእነዚህ ኤሌክትሮኒክ እቃዎች ለእያንዳንዱ ዜጋ ማዳረስ ቀርቶ በንጽጽር ከብዙ የአፍሪካ አገሮችም ባነሰ ደረጀ እንደሆነች ቢነገርም የኢል-ቆሻሻ መዘዝ ለማንሳት ግን ጊዜው አሁን ነው።