Friday, February 3, 2012

ሰነድ ወደ መሬት ሲወርድ

(ጌታቸው አሰፋ፤ ጥር 5 ቀን  2004 ዓ.ም.) የዛሬ ሁለት ሳምንት በወጣው ጽሑፌ ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት በደርባን ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ይፋ ባደረገው በእንግሊዝኛ  የቀረበው “የኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ስልት” ሰነድ ላይ በመመሥረት የሰነዱን ይዘት በወፍ በረር ተመልክተን ነበር።
ለዛሬ በዚህ ሰነድና በአምስት ዓመቱ የዕድገትና ውልጠት ዕቅድ ሰነድ ላይ ስለ ደን ጥበቃና ልማት የተባለውንና መሬት ላይ እየተደረገ ካለው ጋር እንመለከታለን።

‘የአይበገሬውና የአረንጓዴው ኢኮኖሚ’ ሰነድ


(ጌታቸው አሰፋ፤ ታኅሣሥ 21 ቀን  2004 ዓ.ም.)ቅድመ ነገር፡ እንኳን ለአዲስ ጉዳይ አምስተኛ ዓመት አደረሳችሁ። አዘጋጆችም እንኳን ደስ ያላችሁ። ወደ ዛሬው ጉዳይ ስንመለስ…
በኅዳሩ የደርባን ደቡብ አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ወቅት ከተካሄዱት ነገሮች መካከል በኢትዮጵያ መንግሥት  “ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ” በሚል ርእስ የተዘጋጀው ሰነድ ምረቃ ነው። በዛሬው እትም ስለ ሰነዱ ማንሳት

ይዘት አልባው የደርባን ስምምነት


(ታኅሣሥ 7 2004 ዓ.ም. ጌታቸው አሰፋ)የድርድሩ ሂደት ሰኞ ኅዳር 18 ከተጀመረ በኋላ ለአንድ ሳምንት ያህል የተካሄደው ከየአገራቱ በተሰባሰቡት ኤክስፐርቶች አማካይነት ነበር። ሚኒስትሮች በሁለተኛው ሳምንት ማክሰኞ ኅዳር 26 ወደ ደርባን ሲገቡ በከፍተኛ ባለስልጣናት ደረጃ ድርድሩ ቀጠለ። መጀመሪያ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ መሠረት አርብ ኅዳር 29 እንዲያበቃ ስለነበር አርብ ይደረግ የነበረው ድርድር በጣም እየከረረ መጥቶ የመጀመሪያው የስምምነት ረቂቅ ቀረበ። ረቂቁ ከቻይና፤ ከህንድና

ደርባን፡ለኪዮቶ ዳግም ሕይወት ወይስ ሞት


(ጌታቸው አሰፋ, ኅዳር  23  ቀን 2004 ዓ.ምከ12 000 በላይ ልዑካን፤የአካባባቢ ጉዳይ አቀንቃኞችና ተቆርቋሪዎች፤ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና ጋዜጠኞች በዚህ ሳምንት ሰኞ ኅዳር 18  የተጀመረውን 17ኛው የአየር ንብረት ለውጥ ባለጉዳይ አካላት ጉባኤን ምክንያት በማድረግ ደርባን ከተማ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ተገኝተዋል። በዛው ቀን

2 ዲግሪ ሴንትግሬድ፤100 ቢልዮን ዶላር

(ጌታቸው አሰፋ, ኅዳር  9  ቀን 2004 ዓ.ም) ባለፈው ጽሑፍ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር የተያያዘውን ሳይንስ ተመልክተናል። ዛሬም በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ዙሪያ ነው የሚጻፈው።  ከዘጠኝ ቀን በኋላ ማለትም የፊታችን ህዳር 18 17ኛው የአየር ንብረት ለውጥ ባለጉዳይ አካላት ጉባኤ በደቡብ አፍሪካ ደርባን ከተማ ይጀመራል። በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ የሚጠናቀቅ ከሆነ ጉባኤው እስከ ህዳር 29 ይቆያል። በአውሮፓ ህብረት ለረጅም ጊዜ ሲገፋበት የነበረው የሁለት ዲግሪ ሴንትግሬድ(ቅድመ ኢንዱስትሪ አብዮት ከነበረው ጋር ሲነጻጸር) ቀይ መስመር

Saturday, November 12, 2011

350 የካርበን ዳይኦክሳይድ ፊኛዎች?


(ጌታቸው አሰፋ)ይህ ካለፈው የቀጠለ በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ የሚያጠነጥነው ጽሑፍ ነው። ለዛሬ ስለ ሳይንስ በተቻለ መጠን ቀለል አድርገን እናወራለን። የአየር ንብረት ለውጥ ማለት በዓለም ደረጃና በረጅም ጊዜ የሚታዩ የለውጥ መገለጫ የሆኑት የከባቢ አየር ሙቀት፤ የዝናብ መጠንና የመሳሰሉት መገለጫዎች መለወጥ ማለት ነው። በአንድ ቦታና በአጭር ጊዜ ያለው የአየር ሁኔታ ለውጥ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ሊገናኝም ላይገናኝም ይችላል። 
የመስተዋታዊ ቤተ-ተክል ጠንቅ
የአየር ንብረት ለውጥ ሉላዊ ሞቅታ ተብሎም ይጠራል። ለውጡም የሚገለጸው በዓለም የከባቢ አየር አማካይ ሙቀት መጨመር ነው። በሌላ በኩል የመስተዋታዊ ቤተ-ተክል ጠንቅ ተብሎም ይታወቃል። ይህን ስም ያገኘው ግድግዳቸውና ጣራቸው ከመስተዋት ወይም ከፕላስቲክ ከሚሰሩት ለአትክልቶች ለአበቦችና ለመሳሰሉት ማልሚያ ከሚሆኑት ቤቶች ጋር በተያያዘ ነው።  በነዚህ ቤቶች የፀሐይ

Saturday, November 5, 2011

የአየር ንብረት ለውጥና ፍኖተ ደርባን


(ጌታቸው አሰፋ)የዛሬውና የቀጣዩ ጽሑፌ ትኩረት በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ ይሆናል። ምክንያት - አለም አቀፉ አስራ ሰባተኛው የአየር ንብረት ለውጥ ባለጉዳይ አካላት ጉባኤ ከፊታችን ህዳር 18 እስከ  ህዳር 29 በደቡብ አፍሪካ ደርባን ከተማ ስለሚካሄድ። 
ላለፉት አስራ አራት ዓመታት የተካሄዱት አለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ ድርድሮች የሚያጠነጥኑት የኪዮቶ ፕሮቶኮል ተብሎ በሚጠራው ስምምነት ዙሪያ ነው። የኪዮቶ ፕሮቶኮል ባለ ሀያ ስምንት አንቀጽና ሁለት አባሪዎች ስምምነት ሲሆን ጃፓን በሚገኘው የኪዮቶ ከተማ ታህሳስ ሁለት 1990 .. የጸደቀ ነው።