Saturday, April 28, 2012

የት ፈጨሺው?

(ጌታቸው አሰፋ፤ ሚያዝያ 13 ቀን  2004 ዓ.ም.) በሰሜኑ የአገራችን ክፍል በጾም ጊዜ የፍስክ ምግቦች ስም መጠራት የለበትም በሚል እሳቤ ላይ የተመሰረተ የልጆች (የወንድም የሴትም) ጨዋታ አለ። አንድ ልጅ ድንገት ተሳስቶ የፍስክ ምግብ ስም ከጠራ ሌሎች ልጆች ተሽቀዳድመው በቁንጥጫ ይይዙታል። ተቆንጣጩ ጾሙ ሲፈሰክ ለቆንጣጩ የሚሰጠውን የፍስክ ምግብ ጠርቶ ቃል ካልገባ አይለቀቅም። በዚህም ምክንያት ልጆቹ በጾም ወቅት ወሬ ሲያወሩ የፍስክ ነገር እንዳያነሱ መጠንቀቅ አለባቸው ማለት ነው። ይህን የፍስክም የጾምም ምግቦችን የሚያነሳው ጽሑፍ ለመጻፍ አስብ የነበረው ታላቁ የሁዳዴ ጾም ባለፈው ሳምንት ከመጠናቀቁ በፊት ነበር። ይሁንና የአንባቢያን ቁንጥጫ ፈርቼ ሳይሆን አዲስ ጉዳይ የቆየ ጉዳይን እየገፋብኝ ጾሙ ካለቀ በኋላ እነሆ ዛሬ ለመጻ(!) በቅቷል። እንቀጥል።

ኑ መረጃን እንሰብስብ፤ ተደራሽም እናድርገው


(ጌታቸው አሰፋ፤ መጋቢት 29 ቀን  2004 ዓ.ም.) ሰሞኑን በዝቋላ አቦ ገዳም ዙሪያ ያለውና አንድ ለአካባቢው የሆነው (ለአንድ ለእናቱ እንዲሉ) ግርማ ሞገሳሙ ደን በአሳዛኝ ሁኔታ ሲቃጠል ነበር (በጎግል ኧርዝ ካርታ ላይ ደኑን ፍንትው ብሎ ብታዩት አንድ ለአካባቢው የመሆኑ ነገር እጅግ ያሳሳችኋል)።ብዙ ሰው ከአዲስ አበባም ከደብረዘይትም እየተጠራራ ሄዶ ተጋግዞ አጠፋው - በእግዚአብሔር ቸርነት። ይሄ ነገር ከአሁን በፊት የተደጋገመ ክስተት በመሆኑ ለወደፊትም አንድ ነገር ካልተደረገ እንደገና ኧረ ከዛም በላይ ላለመከሰቱ ምንም ዋስትና የለም። እንደገና እንዳይከሰት ለማድረግ የተለያዩ ነገሮች መደረግ እንዳለባቸው በየቦታው ያለ ሰው ሲወያይ ነበር።  

Monday, March 26, 2012

ማኅበራዊ አዛላቂነት

(ጌታቸው አሰፋ፤ መጋቢት 15 ቀን  2004 ዓ.ም.) አዛላቂነት ምጣኔ ሀብታዊ፤ አካባቢያዊና ማኅበራዊ አውታሮች አሉት። ማንኛውም ቴክኖሎጂ፤ ፕሮጄክት ፓሊሲ ወዘተ ከአዛላቂነት አንጻር ስንገመግመው ከእነዚህ ሦስት አውታሮች አኳያ በጎና ጎጂ ተፅዕኖውን ለይተን  አስቀመጥን ማለት ነው። የማኅበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ መስክ በጣም ጠቃሚ ግን በጣም አስቸጋሪ መስክ ነው። የማንኛውም ልማት ጥቅም የሚለካው ተደምሮ ተቀንሶ ለሰው ከሚሰጠው

የአካባቢ ትምህርት ትላንትና ዛሬ


(ጌታቸው አሰፋ፤ መጋቢት 1 ቀን  2004 ዓ.ም.) ድሮ ድሮ በአጋጣሚ ካልሆነ በቀር ሆን ብሎ የአካባቢ ጉዳይን እንደ ትምህርት መስክ መርጦ መማር ብርቅ ነበር። እናም እኔ ወደ አካባቢ ጉዳይ መስክ  የገባሁት የሆነ አጋጣሚ በፈጠረው አጋጣሚ የተነሳ ነበር። ከአስራ ሰባት ዓመታት በፊት እንዲህ ሆነ….

Wednesday, February 29, 2012

ከተማን እንደ ዘአካል


(ጌታቸው አሰፋ፤ የካቲት 17 ቀን  2004 ዓ.ም.) ዘአካል ማለት በአንድ ወይም በሌላ መልኩ የሚገለጽ ሰብሰብ ያለና የራሱ የሆነ አካል (የሚታይም የማይታይም) ያለው ህያው  ማለት ነው - ኦርጋኒዝም የሚባለው ማለት ነው። ዘአካል ያድጋል፡ይራባል። ሲተነኮስ ግብረ መልስ የመስጠት ባህርይም አለው። ዘአካሎች ህያው ሆነው እንዲቀጥሉ የሚያደርጋቸው  ግብአት (ምግብና ኃይል0 ያስፈልጋቸዋል። እነዚህን ግብአቶች በአካባቢያቸው ከሚያገኝዋቸው ምንጮች ገቢ አድርገው ሲያበቁ በግንባንደት ሂደት (ሜታቦሊዝም) አካላቸውን እየገነኑ ወደ አካባቢያቸው ደግሞ ውጣት ይለቃሉ። ይህ ውጣት ጠጣር፡ፈሳሽ ወይም ጋዛማ ሊሆን ይችላል። ኃይልም ሊሆን ይችላል።
ማንኛውም ከተማም ህይወት

Thursday, February 16, 2012

‘አረንጓዴ’ የሕንጻ ግንባታ

(ጌታቸው አሰፋ፤ የካቲት 3 ቀን  2004 ዓ.ም.) ባለፈው እትም ስለ ሕንጻዎቻችን በጀመርነው ጽሑፍ ማጠቃለያ ላይ የሚገነባው እያንዳንዱ ሕንጻ በተቻለ መጠን ከሦስት የአካባቢ ክፍሎች አንጻር እንከን የለሽ ሆኖ መሠራት አለበት ብለን ነበር የፈጸምነው።
የመጀመሪያውና ዋነኛው ከምቹ ስፍራ ልኬት ጋር የሚገናኘው የሕንጻው የውስጠኛው አካባቢ ነው ብለን በውስጥ ምቾት ስር ስለሚካተቱት በቂ ብርሃን፤ ንጹህ አየር፤ ምቹ ሙቀት፤ሽታ አልባ፤ ድምጽና ኬሚካላዊ ልቀት የለሽ ስፍራ ስለ መፍጠር አንሰተን ነበር ያበቃነው።  እስቲ ያዝ ካረግንበት እንልቀቀው።

Friday, February 3, 2012

የሕንጻዎቻችን ጉዳይ

(ጌታቸው አሰፋ፤ ጥር 19 ቀን  2004 ዓ.ም.) ሕንጻዎች ለሃምሳ ወይም ለስድሳ ዓመት ተብለው ይሰራሉ። ይሁን እንጂ ቁጥራቸው ቀላል ያልሆኑ ሕንጻዎች ከመቶ ዓመት በላይ ይቆያሉ። አንድ ትውልድ ማለት ሃያ አምስት ዓመት ማለት ስለሆነ አንድ ሕንጻ ቢያንስ ከተገነባበት ጊዜ ጀምሮ እድሜ ጠግቦ እስኪፈርስ ድረስ