Friday, September 2, 2011

የብክለት ወጥ


(ጌታቸው አሰፋ) አዲስ አበባ የመጀመሪያዋን መኪና ከዛሬ 104 ዓመት በፊት አስተናገደች - ታህሳስ 22 1889 ዓ.ም.። የታርጋ ቁጥሯ D3130 ነበር ተብሏል። አስር ሚልዮን ሕዝብ ያስተዳድሩ የነበሩት አጼ ምኒልክ ቴሌፎንን ወደ አገራችን ባስገቡ ከአራት ዓመት በኋላ ያስገቧት ነች። መጀመሪያ አለማማጃቸው፤ ከዛም እሳቸው፤ ከዛም ሾፌራቸው የነበረው ህንዳዊው ኤዳልጂ የነዷት መኪና ታወጣው የነበረ በካይ - ለምሳሌ ካርቦን-ዳይ-ኦክሳይድ - የአዲስ አበባን ንጹህ አየር በመቀላቀል አሃዱ ያለ አውቶሞቢላዊ በካይ ሆነ - የአገራችን የአካባቢ ብክለት ታሪክ ቅምሻ