Wednesday, June 29, 2011

የችጋርን ቀለበት ሰበራ


(ጌታቸው አሰፋ)ቀለበት የቱ ጋ እንደሚጀምር ለማወቅ ያስቸግራል። እንደ ቀለበት እንዲቀጥል የምንፈልገው በጎ ቀለበት ከሆነ የትስ ቢጀምር ምን ገዶን። መሰበር ያለበት ክፉ ቀለበት ከሆነ ግን የቱ ጋ ነው የጀመረው የሚለውን ጥያቄ መመለስ ወሳኝ ነው። የአገራችን አካባቢ ጉስቁልና እንዲያገግም ለማድረግ በየጊዜው የተለያዩ እርምጃዎች ተወስደዋል።  እየተወሰዱም ነው። ተፈላጊው ውጤት በምንመኘው ልክና ጥራት ግን ለማየት አልቻልንም - እስካሁን። የዚህ እንቆቆልሽ  ቁልፍና የችግራችን መፍትሔ የሚያያዘው የችግሩን ክፉ ቀለበትነት ከመገንዘብ ጋር ነው።  

Wednesday, June 15, 2011

የሚደላን ማመቻመች

(ጌታቸው አሰፋ) ለዛሬ ስለመሬት እጽፋለሁ። ኢትዮጵያችን እንደ አገር ምን ምን እንደሚያስፈልጋት የታወቀ ነው። በራሷ አቅም ህዝቧን መመገብ፤ የውጪ ምንዛሪ ምንጮችን ማስፋት፤ ለዜጎችዋ ቁጥረ-ብዙ የሥራ እድልን መፍጠር፤ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ለማበልጸግ የሚያስችሉ እድሎችን መፍጠርና መጠቀም አለባት። እነዚህን በአጥጋቢ መጠንና ጥራት ማድረግ ያለመቻልዋን የሚያሳብቁ ነባራዊ ተግዳሮቶችን ለመግጠም አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ክስተቶች ግንዛቤ ውስጥ መግባት አለባቸው። በተለይ በዓለም ገበያ ላይ ጥገኛ ከመሆን አልፈን የዓለም ገበያን እኛ ላይ ይሄ ነው በሚባል ደረጃ ጥገኛ ለማድረግ ያልቻልን እኛና መሰል አገሮች ዓለም አቀፋዊ የለውጥ ዜማዎችን ተከትለን እስክስ ማለታችን የግድ ሆኗል።

Wednesday, June 1, 2011

ታሪከ-ቁስ


(ጌታቸው አሰፋ) ታሪክ ሠሪም ባለ ታሪክም ነው ሰው - በሰፊው እንደሚታመንበት። እያንዳንዱ እሴት-አዘል ቁስም (ምርትና አገልግሎት) የራሱ የሆነ ታሪክ አለው -  “ታሪከ ቁስ” ብንለውስ።  አጭር ወይም ረጅም ሊሆን ይችላል። ጥሩም መጥፎም ሊሆን ይችላል። 
የአንድ ምርት ወይም አገልግሎት ታሪክ ሲመረትና ጥቅም ላይ ሲውል የሚያልፍበትን ሂደት የሚያጠቃልል  በጥንተ-ተፈጥሮ  ምንጩ ጀምሮ በጥንተ-ተፈጥሮ ማረፊያው የሚያበቃ ሰንሰለታዊ  ዑደትን የሚያጠቃልል ነው።  ባለሁበት ዩኒቨርስቲ በዚህ ሰንሰለታዊ ዑደት ወቅት በአካባቢ አየር፤ ውኃና የብስ ላይ የሚያደርሰውን ተጽእኖ የማስላትና የመገምገም ዘይቤ ነው “ወንበር ዘርግቼ” ጥናትና ምርምር የማደርገውና ትምህርትም የምሰጠው።