Friday, December 21, 2012

ለመስማማት መስማማት?


(ጌታቸው አሰፋ፤ ታኅሣሥ 6 ቀን  2005 ዓ.ም.)  የዶሃው የአየር ንብረት ጉባኤ ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ ተስፋ አልነበረኝም። ከተጠናቀቀ በኋላም የሚያስደስት ነገር አላገኘሁበትም። ውሳኔዎች ግን ተላልፈዋል - ጥርስ ይኑራቸው አይኑራቸው በጊዜ የምናያቸው። ከውሳኔዎቹ ጥቂት የማይባሉት ከአሁን በፊት በነበሩት ጉባኤያትም የተላለፉ ነበሩ። ስላልተገበሩ ግን አሁንም ‘እናረጋግጣለን’ እና ‘እናጠናክራለን’ ወዘተ የሚል ተጨምሮባቸው ተመልሰው መጥተዋል።  እስቲ የውሳኔውን ዋና ይዘት እንየው።

ልቀቁልን እንጂ አትልቀቁብን - ዶሃ


(ጌታቸው አሰፋ፤ ኅዳር 29 ቀን  2005 ዓ.ም.) የአየር ንብረት ለውጥን እንደ ገዳይ በሽታ ብንቆጥረው ኖሮ ዓለም መታከምና መዳን አለባት የሚለው ላይ እንስማማና ወደ ተግባር እንሄድ ነበር። በዚህ እሳቤ የካርበን ልቀት በሽታ አምጪ ታህዋስያን ልቀት ተደርጎ ከታሰበ ልቀቱ ሲሆን ፈጽሞ እንዳይኖር ካልሆነም በእጅጉ እንዲቀንስ እናደርግ ነበር። ችግሩ ግን በነባራዊው ዓለም የአየር ንብረት ለዋጭ ጋዞች ልቀት ገንዘብ ለማስገኘት በሚደረግ ሂደት የጎንዮሽ ተጽእኖ ሆኖ መከሰቱ ነው። ሌላው ችግር ለቃቂዎች አቅም ያላቸው፤ የሚታመሙት ደግሞ አቅመ አናሳዎች። ቀመሩ ውስጥ ገንዘብና ኢኮኖሚ ባይኖሩበት ኖሮ ይህ ሁሉ የጉባኤ ጋጋታም አያስፈልግም ነበር። ይህ አልሆነምና ስብሰባም ጉባኤም አለ። እነሆ የዶሃው ጉባኤም እንደቀጠለ ነው (ይህ ጽሁፍ እስከተጻፈበት ጊዜ ድረስ)።

የዶሃው ጉባኤ

(ጌታቸው አሰፋ፤ ኅዳር 22  ቀን  2005 ዓ.ም.) ከዚህ ሳምንት ሰኞ ጀምሮ በካታር ዶሃ የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ አስራ ስምንተኛው የባለድርሻዎች ጉባኤ በመካሄድ ላይ ይገኛል። አምና በደርባን ደቡብ አፍሪካ ተደርጎ የነበረው ጉባኤ ቀጣይ ነው። በዓለም አቀፍ ደረጃ ጥርስ ያለው ስምምነት ላይ ለመድረስ የሚያስፈልጉ ነገሮች ሳይንስና ፓለቲካ ናቸው። ሳይንሱ አሁንም በመረጃ እየደለበ እየሄደ ነው። እንዲያውም መሬት ላይ የሚታየው የአየር ንብረት ለውጥ አመልካች ክስተቶች ሳይንስ ይሆናል ካለው ፈጥነው በርክተውና ጎልብተው እየታዩ ነው። በአሜሪካ የኸሪከን ሳንዲ የድርቅ ክስተት፤ የሰሚናዊ ዋልታዊ የበረዶ ግግሮች ከልክ በላይ መቅለጥ፤ የባህር ጠለል ከፍ ማለት፤ የህንድ በኃይለኛ ጎርፍ መጥለቅለቅ፤ የሳህል አገሮች በከፍተኛ ድርቅ መመታት ወዘተ።