Wednesday, February 29, 2012

ከተማን እንደ ዘአካል


(ጌታቸው አሰፋ፤ የካቲት 17 ቀን  2004 ዓ.ም.) ዘአካል ማለት በአንድ ወይም በሌላ መልኩ የሚገለጽ ሰብሰብ ያለና የራሱ የሆነ አካል (የሚታይም የማይታይም) ያለው ህያው  ማለት ነው - ኦርጋኒዝም የሚባለው ማለት ነው። ዘአካል ያድጋል፡ይራባል። ሲተነኮስ ግብረ መልስ የመስጠት ባህርይም አለው። ዘአካሎች ህያው ሆነው እንዲቀጥሉ የሚያደርጋቸው  ግብአት (ምግብና ኃይል0 ያስፈልጋቸዋል። እነዚህን ግብአቶች በአካባቢያቸው ከሚያገኝዋቸው ምንጮች ገቢ አድርገው ሲያበቁ በግንባንደት ሂደት (ሜታቦሊዝም) አካላቸውን እየገነኑ ወደ አካባቢያቸው ደግሞ ውጣት ይለቃሉ። ይህ ውጣት ጠጣር፡ፈሳሽ ወይም ጋዛማ ሊሆን ይችላል። ኃይልም ሊሆን ይችላል።
ማንኛውም ከተማም ህይወት

Thursday, February 16, 2012

‘አረንጓዴ’ የሕንጻ ግንባታ

(ጌታቸው አሰፋ፤ የካቲት 3 ቀን  2004 ዓ.ም.) ባለፈው እትም ስለ ሕንጻዎቻችን በጀመርነው ጽሑፍ ማጠቃለያ ላይ የሚገነባው እያንዳንዱ ሕንጻ በተቻለ መጠን ከሦስት የአካባቢ ክፍሎች አንጻር እንከን የለሽ ሆኖ መሠራት አለበት ብለን ነበር የፈጸምነው።
የመጀመሪያውና ዋነኛው ከምቹ ስፍራ ልኬት ጋር የሚገናኘው የሕንጻው የውስጠኛው አካባቢ ነው ብለን በውስጥ ምቾት ስር ስለሚካተቱት በቂ ብርሃን፤ ንጹህ አየር፤ ምቹ ሙቀት፤ሽታ አልባ፤ ድምጽና ኬሚካላዊ ልቀት የለሽ ስፍራ ስለ መፍጠር አንሰተን ነበር ያበቃነው።  እስቲ ያዝ ካረግንበት እንልቀቀው።

Friday, February 3, 2012

የሕንጻዎቻችን ጉዳይ

(ጌታቸው አሰፋ፤ ጥር 19 ቀን  2004 ዓ.ም.) ሕንጻዎች ለሃምሳ ወይም ለስድሳ ዓመት ተብለው ይሰራሉ። ይሁን እንጂ ቁጥራቸው ቀላል ያልሆኑ ሕንጻዎች ከመቶ ዓመት በላይ ይቆያሉ። አንድ ትውልድ ማለት ሃያ አምስት ዓመት ማለት ስለሆነ አንድ ሕንጻ ቢያንስ ከተገነባበት ጊዜ ጀምሮ እድሜ ጠግቦ እስኪፈርስ ድረስ

ሰነድ ወደ መሬት ሲወርድ

(ጌታቸው አሰፋ፤ ጥር 5 ቀን  2004 ዓ.ም.) የዛሬ ሁለት ሳምንት በወጣው ጽሑፌ ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት በደርባን ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ይፋ ባደረገው በእንግሊዝኛ  የቀረበው “የኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ስልት” ሰነድ ላይ በመመሥረት የሰነዱን ይዘት በወፍ በረር ተመልክተን ነበር።
ለዛሬ በዚህ ሰነድና በአምስት ዓመቱ የዕድገትና ውልጠት ዕቅድ ሰነድ ላይ ስለ ደን ጥበቃና ልማት የተባለውንና መሬት ላይ እየተደረገ ካለው ጋር እንመለከታለን።

‘የአይበገሬውና የአረንጓዴው ኢኮኖሚ’ ሰነድ


(ጌታቸው አሰፋ፤ ታኅሣሥ 21 ቀን  2004 ዓ.ም.)ቅድመ ነገር፡ እንኳን ለአዲስ ጉዳይ አምስተኛ ዓመት አደረሳችሁ። አዘጋጆችም እንኳን ደስ ያላችሁ። ወደ ዛሬው ጉዳይ ስንመለስ…
በኅዳሩ የደርባን ደቡብ አፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ወቅት ከተካሄዱት ነገሮች መካከል በኢትዮጵያ መንግሥት  “ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ” በሚል ርእስ የተዘጋጀው ሰነድ ምረቃ ነው። በዛሬው እትም ስለ ሰነዱ ማንሳት

ይዘት አልባው የደርባን ስምምነት


(ታኅሣሥ 7 2004 ዓ.ም. ጌታቸው አሰፋ)የድርድሩ ሂደት ሰኞ ኅዳር 18 ከተጀመረ በኋላ ለአንድ ሳምንት ያህል የተካሄደው ከየአገራቱ በተሰባሰቡት ኤክስፐርቶች አማካይነት ነበር። ሚኒስትሮች በሁለተኛው ሳምንት ማክሰኞ ኅዳር 26 ወደ ደርባን ሲገቡ በከፍተኛ ባለስልጣናት ደረጃ ድርድሩ ቀጠለ። መጀመሪያ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ መሠረት አርብ ኅዳር 29 እንዲያበቃ ስለነበር አርብ ይደረግ የነበረው ድርድር በጣም እየከረረ መጥቶ የመጀመሪያው የስምምነት ረቂቅ ቀረበ። ረቂቁ ከቻይና፤ ከህንድና

ደርባን፡ለኪዮቶ ዳግም ሕይወት ወይስ ሞት


(ጌታቸው አሰፋ, ኅዳር  23  ቀን 2004 ዓ.ምከ12 000 በላይ ልዑካን፤የአካባባቢ ጉዳይ አቀንቃኞችና ተቆርቋሪዎች፤ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና ጋዜጠኞች በዚህ ሳምንት ሰኞ ኅዳር 18  የተጀመረውን 17ኛው የአየር ንብረት ለውጥ ባለጉዳይ አካላት ጉባኤን ምክንያት በማድረግ ደርባን ከተማ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ተገኝተዋል። በዛው ቀን

2 ዲግሪ ሴንትግሬድ፤100 ቢልዮን ዶላር

(ጌታቸው አሰፋ, ኅዳር  9  ቀን 2004 ዓ.ም) ባለፈው ጽሑፍ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር የተያያዘውን ሳይንስ ተመልክተናል። ዛሬም በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ዙሪያ ነው የሚጻፈው።  ከዘጠኝ ቀን በኋላ ማለትም የፊታችን ህዳር 18 17ኛው የአየር ንብረት ለውጥ ባለጉዳይ አካላት ጉባኤ በደቡብ አፍሪካ ደርባን ከተማ ይጀመራል። በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ የሚጠናቀቅ ከሆነ ጉባኤው እስከ ህዳር 29 ይቆያል። በአውሮፓ ህብረት ለረጅም ጊዜ ሲገፋበት የነበረው የሁለት ዲግሪ ሴንትግሬድ(ቅድመ ኢንዱስትሪ አብዮት ከነበረው ጋር ሲነጻጸር) ቀይ መስመር