Tuesday, January 22, 2013

ዋልያዎች ለዋልያዎች - ዘኳስ ለዘሜዳ

(ጌታቸው አሰፋ፤ ጥር 11 ቀን  2005 ዓ.ም.) ለዛሬ ስለ ሁለት ዋልያዎች እንጽፋለን - የኢትዮጵያችን የብቻዋ ስለሆነ እንስሳው ዋልያና ዋልያ ተብሎ ስለሚጠራው ብሔራዊው የእግር ኳስ ቡድናችን። በተለይ ስለ ሁለተኛው ዋልያ ለመጻፍ ወይም መጻፍ ለመጀመር ዛሬ ምቹ ነው። ብሔራዊ ቡድናችን የያዘውን መጠሪያ ስም ያገኘው ከብርቅየው እንስሳ ‘ዋልያ አይቤክስ’ ስም ነው። የአሰያየም ሂደቱ በተመለከተ ዝርዝር መረጃ የለኝም (እነ ደጉ፤ አዳነና ጀማልም አናውቀውም ሲሉ ሰምቻለሁ)። ዋልያ አይቤክስ የኢትዮጵያ ከኢትዮጵያ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ሊሆን እንደሚችል ግን መገመት ይቻላል። ስለ ሁለቱም ዋልያዎች (ዋልያ ዘሜዳና ዋልያ ዘኳስ) በተራበ ተራ (አሁን ባይርበኝ ኖሮ ‘በተራ በተራ’ ብዬ እጽፈው ነበር) እናነሳና ከዛም መልሰን እናገናኛቸዋለን።

እነሱ ከእኛ ወይስ እኛ ከነሱ?

(ጌታቸው አሰፋ፤ ጥር 4 ቀን  2005 ዓ.ም.) በውጪው ዓለም ገና እና አዲስ ዓመት በስድስት ቀናት ልዩነት የሚከሰቱ ሁለት በዓላት ሲሆን መዘዛቸው ደግሞ እጅግ ከፍተኛ ነው። በምዕራቡ ዓለም የገና በዓል ከጊዜ ወደ ጊዜ ትርጉሙም ሚናውም እየተቀየረ መምጣቱን ማየት ይቻላል። እዚህ ካናዳ ውስጥ በአንድ ትምህርት ቤት ህጻናት ከቤተሰቦቻቸው ለተለያያ ትውልድ የገና በዓል የሚሰጠው ትርጉም ምን እንደነበር ጠይቀው እንዲጽፉ የቤት ስራ ይሰጣቸዋል። አንዱ ቅድመ አያቱን አያቱንና አባቱን ጠይቆ መጣ። ሴቷ ቅድመ አያቱ በዘመናቸው ጊዜ የነበረውንና የገና ብስኩት ላይ ስለሚቀባው ክሬም አንስተው ለዛን ዘመን ውድ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ለገና ብቻ ተቀብቶ ስለሚበሉት እንዴት በጉጉት ይጠብቁት እንደነበርና ያኔ የሰፈር ሰዎች አንድ ላይ ሆነው ያከብሩ እንደነበር አጫወቱት። አባታቸው ሚንስተር የነበሩት አያቱ ደግሞ የገና በዓል ለሳቸው ዘመን ሰዎች ጎዳና ተዳዳሪዎችን የመርጃ፤ ቤተ ክርስቲያን ሄደው ዝማሬ ማቅረቢያና ጎረቤታሞች ምግብና ደስታ የሚጋሩበት እርስ በርስ እየተደጋገፉ የሚያከብሩበት በዓል እንደነበር ነገሩት። አባቱን ሲጠይቅ ያገኘው መልስ ደግሞ የገና በዓል አከባበር ሌላ ቅርጽና ይዘት መምጣቱን ማየት የሚያስችል ነበር። አባትዬው ስለ አሻንጉሊቶችና ትልልቅ የፕላስቲክ መጫዎቻዎች እንደስጦታ መስጠት ዋነኛው የበዓሉ መገለጫ እየሆኑ መምጣታቸውንና ከዚህም ጋር በተያያዘ  ወላጆች ስጦታዎችን ለመግዛት አቅም በሚያጡበት ጊዜ እንዴት ጫናም ሀዘንም ይሰማቸው እንደነበር አጫወቱት።

Tuesday, January 8, 2013

ከጤንነት የሚሻል ሕክምና የለም

(ጌታቸው አሰፋ፤ ታኅሣሥ 20 ቀን  2005 ዓ.ም.)  ዛሬ የምጽፍበት ጉዳይ ከአረንጓዴ ጉዳይ ጋር ምን አገናኘው ለምትሉ አስቀድሜ መልስ ልስጥ። በአካባቢ ጥበቃም ሆነ በኃይል አቅርቦትና ፍጆታ ዙሪያ በአገሪቱ መዋዕለ ንዋይ ፈሶባቸው የሚሰሩ ስራዎች ወጪ ቆጣቢ ሆነው ውጤታማ እንዲሆኑ ካስፈለገ ከእውቀት አኳያ አንዱን ሳይጥል ሌላውን ሳያንጠለጥል መሆን አለበት። ከዚህ በላይ ደግሞ የማንኛውም አገር ልማታዊ ጉዞ በእውቀት ላይ መመስረት አለበት። በዚህ ሁሉም ሰው ከሞላ ጎደል ይስማማል። እውቀት ደግሞ ከመማር ይገኛል። በዚህም ብዙ ልዩነት አይኖርም። ጥያቄ የሚነሳው ግን ‘መማር ምን ማለት ነው?’ ‘ሰው የትና ከማን ይማራል?’ ‘ከየትና ከማንስ መማር አለበት?’ በሚሉት ዙሪያ ላይ ነው። በአገራችን በየእርከኑ መደበኛ ትምህርት ቤትና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ገብቶ የሚማረው ሰው ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ ይገኛል። ለፈጣንና አዛላቂ እድገት የተማረ ሰው ቁጥር መጨመሩ አስፈላጊ ነውና ደግ ነው።

Friday, December 21, 2012

ለመስማማት መስማማት?


(ጌታቸው አሰፋ፤ ታኅሣሥ 6 ቀን  2005 ዓ.ም.)  የዶሃው የአየር ንብረት ጉባኤ ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ ተጠናቋል። በጉባኤው ላይ ተስፋ አልነበረኝም። ከተጠናቀቀ በኋላም የሚያስደስት ነገር አላገኘሁበትም። ውሳኔዎች ግን ተላልፈዋል - ጥርስ ይኑራቸው አይኑራቸው በጊዜ የምናያቸው። ከውሳኔዎቹ ጥቂት የማይባሉት ከአሁን በፊት በነበሩት ጉባኤያትም የተላለፉ ነበሩ። ስላልተገበሩ ግን አሁንም ‘እናረጋግጣለን’ እና ‘እናጠናክራለን’ ወዘተ የሚል ተጨምሮባቸው ተመልሰው መጥተዋል።  እስቲ የውሳኔውን ዋና ይዘት እንየው።

ልቀቁልን እንጂ አትልቀቁብን - ዶሃ


(ጌታቸው አሰፋ፤ ኅዳር 29 ቀን  2005 ዓ.ም.) የአየር ንብረት ለውጥን እንደ ገዳይ በሽታ ብንቆጥረው ኖሮ ዓለም መታከምና መዳን አለባት የሚለው ላይ እንስማማና ወደ ተግባር እንሄድ ነበር። በዚህ እሳቤ የካርበን ልቀት በሽታ አምጪ ታህዋስያን ልቀት ተደርጎ ከታሰበ ልቀቱ ሲሆን ፈጽሞ እንዳይኖር ካልሆነም በእጅጉ እንዲቀንስ እናደርግ ነበር። ችግሩ ግን በነባራዊው ዓለም የአየር ንብረት ለዋጭ ጋዞች ልቀት ገንዘብ ለማስገኘት በሚደረግ ሂደት የጎንዮሽ ተጽእኖ ሆኖ መከሰቱ ነው። ሌላው ችግር ለቃቂዎች አቅም ያላቸው፤ የሚታመሙት ደግሞ አቅመ አናሳዎች። ቀመሩ ውስጥ ገንዘብና ኢኮኖሚ ባይኖሩበት ኖሮ ይህ ሁሉ የጉባኤ ጋጋታም አያስፈልግም ነበር። ይህ አልሆነምና ስብሰባም ጉባኤም አለ። እነሆ የዶሃው ጉባኤም እንደቀጠለ ነው (ይህ ጽሁፍ እስከተጻፈበት ጊዜ ድረስ)።

የዶሃው ጉባኤ

(ጌታቸው አሰፋ፤ ኅዳር 22  ቀን  2005 ዓ.ም.) ከዚህ ሳምንት ሰኞ ጀምሮ በካታር ዶሃ የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ አስራ ስምንተኛው የባለድርሻዎች ጉባኤ በመካሄድ ላይ ይገኛል። አምና በደርባን ደቡብ አፍሪካ ተደርጎ የነበረው ጉባኤ ቀጣይ ነው። በዓለም አቀፍ ደረጃ ጥርስ ያለው ስምምነት ላይ ለመድረስ የሚያስፈልጉ ነገሮች ሳይንስና ፓለቲካ ናቸው። ሳይንሱ አሁንም በመረጃ እየደለበ እየሄደ ነው። እንዲያውም መሬት ላይ የሚታየው የአየር ንብረት ለውጥ አመልካች ክስተቶች ሳይንስ ይሆናል ካለው ፈጥነው በርክተውና ጎልብተው እየታዩ ነው። በአሜሪካ የኸሪከን ሳንዲ የድርቅ ክስተት፤ የሰሚናዊ ዋልታዊ የበረዶ ግግሮች ከልክ በላይ መቅለጥ፤ የባህር ጠለል ከፍ ማለት፤ የህንድ በኃይለኛ ጎርፍ መጥለቅለቅ፤ የሳህል አገሮች በከፍተኛ ድርቅ መመታት ወዘተ።

Sunday, November 25, 2012

በሌለ በሬ ማረስ?


(ጌታቸው አሰፋ፤ ኅዳር 15  ቀን  2004 ዓ.ም.)ስለ ‘ያ ትውልድ’ና ‘ይሄ ትውልድ’ ከመጻፍ አስቀድሞ ‘ያ ትውልድ እና ይሄ ትውልድ ስንል ምን ማለታችን ነው?’ የሚለውን ጥያቄ መመለስ ተገቢ ነው። በተለመደው አባባል በ1960ቹ መጀመሪያ አጋማሽ ውስጥ ይካሄዱ በነበሩት የተማሪዎች እንቅስቃሴዎች ወቅት እድሜያቸው ቢያንስ ለአቅመ-መሳተፍ የደረሱ ሰዎች ስብስብን ነው ‘ያ ትውልድ’ የምንለው።
ላላ ስናደርገው ….የእድሜ መስፈርቱ እንዳለ ሆኖ ቀጥሎ ያለውን አይነት ግጥም የሚገጥም ሰው ወይም እንዲህ ተብሎ የተጻፈ ግጥምን ማንበብ አሁን ድረስ የሚመስጠው ሰው አባል የሆነበት ትውልድ ማለት ነው ልንልም እንችላለን።