Wednesday, July 27, 2011

የነፍስ ቁርጥማት


(ጌታቸው አሰፋ)ድርቅ አጥቢያዊ መነሻና ምክንያት አለው። አሁን አሁን ደግሞ እንደ ሉላዊ አባባሽ ምክንያትና መነሻ የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ(በካባቢ አየር ሙቀት መጨመር የሚገለጸው) ይጠቀሳል። ኢትዮጵያ ውስጥ ድርቅ መከሰት የጀመረው የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ሰውኛ መንስኤው ይበልጥ እየተረጋገጠ ከመምጣቱ ቢያንስ መቶ ዓመታት በፊት ነው። በመፍትሔ ደረጃ አጥቢያዊ መነሻው ላይ ስናተኩር የሚጨበጥ ነገር ማድረግ እንችላለን። ሉላዊ መነሻችን እንደ አገር ብቻችንን በተናጠል ከኃሌ-ኵሉ ሆነን የምንፈታው አይደለምና። በዛ ላይ አጥቢያዊ ምንጩን ስናደርቅ ሉላዊ ድርሻችንን ተወጣን ማለት ስለሚሆን አሪፍ ነው።
ለእውቀት ያህል ግን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ በአንዳንድ ቦታዎች ድርቅን ሲያባብስ  በሌሎች ቦታዎች ደግሞ የጎርፍ መጥለቅለቅን ያመጣል (ሌላ ጊዜ እመለስበታለሁ)። 

Wednesday, July 13, 2011

“እቃሻሻ”

(ጌታቸው አሰፋ)(ደረቅ) ቆሻሻን የሆነ እቃ የቅርብ ዘመድ አድርገን ልንቆጥረው እንችላለን። ዝምድናው በተለያየ መልኩ ሊገለፅ የሚችል ነው። የእቃው አያቶች የሆኑትን ጥሬ ዕቃዎች ከማልማት ሂደት ጋር የሚገኝ ቆሻሻ አለ። እቃው ሲመረት የሚፈጠርም አለ። እቃው ጥቅም ላይ ሲውልም በማርጀት ወይም በመበላሸት ወይም ተጠቃሚው በሌላ ምክንያት እቃውን መጠቀም ሲያቆም የሚፈጠረውም ሌላው ነው።
የቆሻሻ መጥፎነት  - መጥፎ ከሆነ - ከመጠኑና ከይዘቱ ጋር የሚተሳሰር ነው። “ቆሻሻህን አሳየኝና ማንነትህን እነርግርሃለሁ” የሚል አባባል አለ ሲባል ከሰማን ኖረም አልኖረም አባባሉ ትክክል ስለሆነ የለም ብለን ባንከራከር ይሻላል።