Thursday, October 13, 2011

ባለአረንጓዴ ቀበቶ ጀግና


(ጌታቸው አሰፋ) ዛሬ ይህ አምድ ኬንያዊቷን ዋንጋሪ ማታይን ያስባል። ዋንጋሪ ሙታ ሜሪ ጆ ማታይ ከሰባ አንድ ዓመታት በፊት በሞኞች ቀን(April 1) የተወለዱ ልባም ሴት ነበሩ።  የመጀመሪያ ዲግሪያቸውንና ሁለተኛ ዲግሪያቸውን በስነ-ህይወት ከአሜሪካ ዩኒቨርስቲዎች የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ደግሞ በእንስሳት ጤና ሳይንስ ስነ-ብልት ጥናት ከናይሮቢ ዩኒቨርስቲ አግኝተዋል። እሁድ መስከረም አስራ አራት 2004 ዓ.ም. በሞት ተለዩን። ሥራቸው ግን ከመንደራቸው፤ ከአገራቸውና ከአህጉራቸው አልፎ ከፍተኛ ዓለም አቀፋዊ እውቅናን ያገኘ ህያው ሥራ ሆኖ ይቀጥላል።  

ቀመሩ እንዲሰምር

(ጌታቸው አሰፋ)ስለ ግብርና እጽፋለሁ - ለዛሬ። መንግሥት ሁለት የማዳበሪያ ፋብሪካዎችን እገነባለሁ ማለቱ ነው መነሻዬ። መልካም ዜና ነው። እስቲ ወደ ኋላ ከመቶ ሃምሳ ዓመታት በላይ እንንደርደር።
ከአጼ ቴዎድሮስ ጋር ለአሥር ዓመታት በአገራችን የኖረ ስዊዘርላንዳዊው ሚሶንያዊ ቴዎፍሎስ ቫልድማየር በዚህ ወር ግን ከ153 ዓመታት በፊት ወደ አቢስኒያ ተጓዘ። ከአምስት ወር በኃላም ገባ። ይህ ከሆነ ከሀያ ስምንት ዓመታት በኋላም ስለአሥር ዓመት ቆይታው መጽሐፍ ጻፈ (የተሳሳቱ መረጃዎች ያሉበት)። በመጽሐፉ የዛሬው ጉዳዬ ስለሆነው እርሻችንና ተያያዥ ነገሮችን በተመለከተ የተጻፈውንና የተሳሳተ ነው የሚያስብል ነገር ያላገኘሁለትን ወደ አማርኛ እንዲህ መልሼዋለሁ። 

በዓል - ከጓዳ እስከ አካባቢ

(ጌታቸው አሰፋ) እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ። ከአንድ ሁለት ሳምንት በፊት የሸገር ራዲዮ “ዳጉ አዲስ”ን እያዳመጥኩ ነበር- በኢንተርኔት የቀጥታ ስርጭት። ወንዶች ሴቶችን በቤት ሥራ ማገዝ አለባቸው ወይስ የለባቸውም በሚል ርዕስ ስር ከተለያዩ ወጣቶች ጋር ቃል ምልልስ ያደርጋሉ - ዳጉዎች። ሁለት ወንድ ወጣቶች ቤታቸው ውስጥ ሽሮ ወጥ ሲሠሩ ከፕሮግራሙ አዘጋጆች አንዱ ተገኝቶ አሠራራቸውን በድምጽ ለራዲዮ አድማጮች ያስተላልፋል። ልጆቹና ጋዜጠኛው እያወሩ ከጀርባቸው አንድ አውራ ዶሮ ድምጹን ከፍ አድርጎ አሰምቶ ይጮሃል። የአሥር ወር ልጄን አየሁት። እየጮኸ ያለው አውራ ዶሮ መሆኑን ሊያውቅ እንደማይችል አሰብኩ። የእሱ አስተዳደግ በአካል ከሚታይ አውራ ዶሮ ጋር ያለው ርቀት የኔ አስተዳደግ ከአውራ ዶሮ ጋር ከነበረው ቁርኝት ጋር ያለው ልዩነት እያስደመመኝ ዓመት በዓል በመጣ ቁጥር ስለማስበው ነገር ማብሰልሰል ጀመርኩ - ስለ ዶሮ ወጥ።