Wednesday, July 27, 2011

የነፍስ ቁርጥማት


(ጌታቸው አሰፋ)ድርቅ አጥቢያዊ መነሻና ምክንያት አለው። አሁን አሁን ደግሞ እንደ ሉላዊ አባባሽ ምክንያትና መነሻ የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ(በካባቢ አየር ሙቀት መጨመር የሚገለጸው) ይጠቀሳል። ኢትዮጵያ ውስጥ ድርቅ መከሰት የጀመረው የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ሰውኛ መንስኤው ይበልጥ እየተረጋገጠ ከመምጣቱ ቢያንስ መቶ ዓመታት በፊት ነው። በመፍትሔ ደረጃ አጥቢያዊ መነሻው ላይ ስናተኩር የሚጨበጥ ነገር ማድረግ እንችላለን። ሉላዊ መነሻችን እንደ አገር ብቻችንን በተናጠል ከኃሌ-ኵሉ ሆነን የምንፈታው አይደለምና። በዛ ላይ አጥቢያዊ ምንጩን ስናደርቅ ሉላዊ ድርሻችንን ተወጣን ማለት ስለሚሆን አሪፍ ነው።
ለእውቀት ያህል ግን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ በአንዳንድ ቦታዎች ድርቅን ሲያባብስ  በሌሎች ቦታዎች ደግሞ የጎርፍ መጥለቅለቅን ያመጣል (ሌላ ጊዜ እመለስበታለሁ)። 

Wednesday, July 13, 2011

“እቃሻሻ”

(ጌታቸው አሰፋ)(ደረቅ) ቆሻሻን የሆነ እቃ የቅርብ ዘመድ አድርገን ልንቆጥረው እንችላለን። ዝምድናው በተለያየ መልኩ ሊገለፅ የሚችል ነው። የእቃው አያቶች የሆኑትን ጥሬ ዕቃዎች ከማልማት ሂደት ጋር የሚገኝ ቆሻሻ አለ። እቃው ሲመረት የሚፈጠርም አለ። እቃው ጥቅም ላይ ሲውልም በማርጀት ወይም በመበላሸት ወይም ተጠቃሚው በሌላ ምክንያት እቃውን መጠቀም ሲያቆም የሚፈጠረውም ሌላው ነው።
የቆሻሻ መጥፎነት  - መጥፎ ከሆነ - ከመጠኑና ከይዘቱ ጋር የሚተሳሰር ነው። “ቆሻሻህን አሳየኝና ማንነትህን እነርግርሃለሁ” የሚል አባባል አለ ሲባል ከሰማን ኖረም አልኖረም አባባሉ ትክክል ስለሆነ የለም ብለን ባንከራከር ይሻላል።

Wednesday, June 29, 2011

የችጋርን ቀለበት ሰበራ


(ጌታቸው አሰፋ)ቀለበት የቱ ጋ እንደሚጀምር ለማወቅ ያስቸግራል። እንደ ቀለበት እንዲቀጥል የምንፈልገው በጎ ቀለበት ከሆነ የትስ ቢጀምር ምን ገዶን። መሰበር ያለበት ክፉ ቀለበት ከሆነ ግን የቱ ጋ ነው የጀመረው የሚለውን ጥያቄ መመለስ ወሳኝ ነው። የአገራችን አካባቢ ጉስቁልና እንዲያገግም ለማድረግ በየጊዜው የተለያዩ እርምጃዎች ተወስደዋል።  እየተወሰዱም ነው። ተፈላጊው ውጤት በምንመኘው ልክና ጥራት ግን ለማየት አልቻልንም - እስካሁን። የዚህ እንቆቆልሽ  ቁልፍና የችግራችን መፍትሔ የሚያያዘው የችግሩን ክፉ ቀለበትነት ከመገንዘብ ጋር ነው።  

Wednesday, June 15, 2011

የሚደላን ማመቻመች

(ጌታቸው አሰፋ) ለዛሬ ስለመሬት እጽፋለሁ። ኢትዮጵያችን እንደ አገር ምን ምን እንደሚያስፈልጋት የታወቀ ነው። በራሷ አቅም ህዝቧን መመገብ፤ የውጪ ምንዛሪ ምንጮችን ማስፋት፤ ለዜጎችዋ ቁጥረ-ብዙ የሥራ እድልን መፍጠር፤ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ለማበልጸግ የሚያስችሉ እድሎችን መፍጠርና መጠቀም አለባት። እነዚህን በአጥጋቢ መጠንና ጥራት ማድረግ ያለመቻልዋን የሚያሳብቁ ነባራዊ ተግዳሮቶችን ለመግጠም አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ክስተቶች ግንዛቤ ውስጥ መግባት አለባቸው። በተለይ በዓለም ገበያ ላይ ጥገኛ ከመሆን አልፈን የዓለም ገበያን እኛ ላይ ይሄ ነው በሚባል ደረጃ ጥገኛ ለማድረግ ያልቻልን እኛና መሰል አገሮች ዓለም አቀፋዊ የለውጥ ዜማዎችን ተከትለን እስክስ ማለታችን የግድ ሆኗል።

Wednesday, June 1, 2011

ታሪከ-ቁስ


(ጌታቸው አሰፋ) ታሪክ ሠሪም ባለ ታሪክም ነው ሰው - በሰፊው እንደሚታመንበት። እያንዳንዱ እሴት-አዘል ቁስም (ምርትና አገልግሎት) የራሱ የሆነ ታሪክ አለው -  “ታሪከ ቁስ” ብንለውስ።  አጭር ወይም ረጅም ሊሆን ይችላል። ጥሩም መጥፎም ሊሆን ይችላል። 
የአንድ ምርት ወይም አገልግሎት ታሪክ ሲመረትና ጥቅም ላይ ሲውል የሚያልፍበትን ሂደት የሚያጠቃልል  በጥንተ-ተፈጥሮ  ምንጩ ጀምሮ በጥንተ-ተፈጥሮ ማረፊያው የሚያበቃ ሰንሰለታዊ  ዑደትን የሚያጠቃልል ነው።  ባለሁበት ዩኒቨርስቲ በዚህ ሰንሰለታዊ ዑደት ወቅት በአካባቢ አየር፤ ውኃና የብስ ላይ የሚያደርሰውን ተጽእኖ የማስላትና የመገምገም ዘይቤ ነው “ወንበር ዘርግቼ” ጥናትና ምርምር የማደርገውና ትምህርትም የምሰጠው።

Wednesday, May 18, 2011

መከላከያና አካባቢ

(ጌታቸው አሰፋ) ጠበብ አድርገን ካየነው ኦሳማ ቢን ላደንን የመግደል ተልእኮ የፈጸሙት 4 ሄሊኮፕቶሮች፤ 24 ወታደሮች (እንደ ቆጣሪው ቢለያይም) እና አንድ “ካይሮ” የተሰኘ ስልጡን ውሻ ናቸው። አስፍተን ካየነው ግን ቢን ላደንን አንዴ የተፈጥሮ አካባቢን ደጋግሞ እየገደለ ያለው ከአቦታባድ ተልእኮ በስተጀርባ ያለው በዘመናዊ ውስብስብ ቴክኖሎጂና በመደበኛ የስለላ አውታሮች የሚታገዘው ግዙፉ የአሜሪካ መከላከያ ነው። የአሜሪካ መከላከያ በዓለማችን ከፍተኛና ስርጭተ-ሰፊ አካባቢ በካይና አጎስቋይ ተቋም የመሆኑ ነገር ነው የዛሬ “የአረንጓዴ ጉዳይ” መቆያችን። 

Thursday, May 5, 2011

የ”ጉ” ቤት ለግብጾች


(ጌታቸው አሰፋ)ወደ ጀልባው የገባሁት ዘግይቼ ነበር። ያልተያዘ ወንበር ያለበት ጠረጴዛ ስፈልግ አንድ ብቻውን የተቀመጠ ሰው አየሁና ሄጄ ተቀላቀልኩ። ተዋወቅኩት። ይህ የሆነው የዛሬ ሰባት ዓመት ካናዳ ቶሮንቶ ነው። ከየአገሩ የተሰባሰብን የኮንፈረንስ ተሳታፊዎች ማብቂያ ላይ በኦንታሪዮ ሐይቅ እየተዟዟርን ለምንበላው እራት ነው ጀልባው ውስጥ የተገኘነው። “ከየት ነህ?” አልኩት። “ከዚሁ ከካናዳ ነኝ። ቶሮንቶ ዩኒቨርሲቲ ነው የማስተምረው” አለኝ። እኔም ተጠየቅኩ። “ከኢትዮጵያ ነኝ። አሁን ግን ስዊድን ነው ያለሁት” ብዬ የነበርኩበትን ዩኒቨርሲቲ ነገርኩት። ጠይምነቱ “መሠረትህ ግን ከየት ነው?” እንድለው ገፋፋኝ። ገና “ከግብጽ” ከማለቱ ሌላ ጥያቄ አስከተልኩ። “በጣም ጥሩ አጋጣሚ….. በመንግሥት ደረጃ ሳይሆን በተራ ግብጻዊ ደረጃ ስለአባይ የሚሰማችሁን ነገር እስቲ ንገረኝ።” የፊቱ  ቀለም ተቀያየረ።